CURRENT

ሲሲቲቭ የተሰኘው የቴሌቭዥን ጣቢያ ዛሬ እንደዘገበው የአውሮፓ ሕብረት በ12 የአፍሪካ ሃገራት አየር መንገዶች ላይ በሕብረቱ የአየር ክልሎች

By Admin

June 21, 2016

ሲሲቲቭ የተሰኘው የቴሌቭዥን ጣቢያ ዛሬ እንደዘገበው የአውሮፓ ሕብረት በ12 የአፍሪካ ሃገራት አየር መንገዶች ላይ በሕብረቱ የአየር ክልሎች እንዳይበሩ እገዳ አስተላለፈ::

ሕብረቱ ኤርትራን ጨምሮ በ12 ሃገራት ላይ እገዳውን ሲጥል ሃገራቱም

1ኛ . ቤኒን 2ኛ. ኮንጎ ሪፐብሊክ 3ኛ. ዴሞክራሲያ ሪፐብሊክ ኮንጎ 4ኛ. ጅቡቲ 5ኛ. ኢኳቶሪያል ጊኒ 6ኛ. ጋቦን 7ኛ. ላይቤሪያ 8ኛ. ሊቢያ 9ኛ. ሞዛምቢክ 10ኛ. ሴራሊዮን 11ኛ. ሱዳን ናቸው::

የአውሮፓ ሕብረት የ214 አየር መንገዶችን የደህንነት ደረጃ የመረመረ ሲሆን ከአፍሪካ 12 እንዲሁም ከሌሎች ዓለም ሃገራት 7 በጥቅሉ የ19 ሃገራትን አየር መንገዶች አግዷል::

ለረዥም ጊዜያት እገዳ ተጥሎበት የቆየው የዛምቢያና የማዳጋስካር አየር መንገዶች በአውሮፓ እንዲበሩ የተፈቀደ ሲሆን ከላይ የተጠቀሱት ሃገራት አየር መንገዶች ለመንገደኞች ደህንነት አስጊዎች ናቸው በሚል በክልሉ እንዳይበሩ መታገዱን  ከሲሲቲቭ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል:;