Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ባለፈው ወር ከፈረንሳይ ወደ ካይሮ እየተጓዘ እያለ በሜዲትራኒያን ባህር ላይ የተከሰከሰው የግብፅ አየር መንገድ አውሮፕላን ስብርባሪ አካል መገኘቱ

0 617

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ባለፈው ወር ከፈረንሳይ ወደ ካይሮ እየተጓዘ እያለ በሜዲትራኒያን ባህር ላይ የተከሰከሰው የግብፅ አየር መንገድ አውሮፕላን ስብርባሪ አካል መገኘቱ ቢቢሲን ጠቅሶ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል፡፡

ግብፃውያን መርማሪዎች ናቸው የአውሮፕላኑ ክፍል የሆነ ስብርባሪ መገኘቱን ያስታወቁት።

ስብርባሪ አካሉ የሚገኝበት አቅጣጫም ተለይቷል።

ጥልቅ የባህር ውስጥ ፍለጋ ጀልባም የስብርባሪ አካሉን ምስል ለመጀመሪያ ጊዜ ልካለች ተብሏል።

የበረራ ቁጥሩ ኤም ኤስ 804 የሆነው የግብፅ አየር መንገድ አውሮፕላን በፈረንጆቹ ግንቦተ 19 ነበር 66 መንገደኞችን አሳፍሮ ከፓሪስ ወደ ካይሮ እየተጓዘ እያለ በሜዲትራኒያን ባህር የተከሰከሰው።

ኤርባስ ኤ320 አውሮፕላኑ ምንም መልዕክት ሳይጠቁም ከግሪክ እና ግብፅ የራዳር እይታዎች ውጪ መሆኑ ይታወሳል።

በመከስከስ አደጋው 66ቱም መንገደኞች ህይወታቸው አልፏል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy