Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኢትዮጵያ ዘላቂ የልማት ግቦችን እንደምታሳካ ጠ/ ሚ ኃይለማርያም ገለጹ

0 513

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኢትዮጵያ ዘላቂ የልማት ግቦችን እንደምታሳካ ጠ/ ሚ ኃይለማርያም ገለጹ

ሰኔ 09፣ 2008

ኢትዮጵያ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ የተቀመጡ አጀንዳዎችን የመፈፀም ብቃት እንዳላት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለፁ፡፡

የአውሮፓ የልማት ጉባኤ በቤልጀም ብራሰልስ እየተካሄደ ነው፡፡

በመድርኩ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የልማት ግቦችን ለማሳካት ከሀገሪቱ ዕቅዶች ጋር በማስተሳሰር እየሰራች ነው፡፡

እያስመዘገበችው ያለው የኢኮኖሚ እድገትም ግቦቹን ለማሳካት ያስችላታል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

ለዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት ከመንግስት ጥረት ጎን ለጎን የዓለም አቀፉ ማህበረስብ አጋርነት እንደሚያስፈልግም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል፡፡

የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ፌዴሪካ ሞጎሪኒ በበኩላቸው ህብረቱ ግቦችን የሚያሳካ ትብብር ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ ጉባኤ ላይ የተለያዩ አገራት መሪዎች ለዘላቂ የልማት ግቦች ስኬታማነት  ያከናወኑትን ተግባራት የተመለከተ ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡

ሪፖርተር፡- ብሩክ ያሬድ( ከቤልጄም ብራስልስ)

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy