Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ18 ቢሊዮን ብር ብድር ሰጠ

0 992

Get real time updates directly on you device, subscribe now.


ሰኔ 08፣2008

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ መንግስት ለአምስት ፕሮጀክቶች ማስፋፊያና ማስፈጸሚያ የሚውል የ18 ቢሊዮን ብር ብድር ሰጠ።

ብድሩ ለከፍተኛ ትምህርትና ለኤሌክትሪክ መሥመሮች ማስፋፊያ፣ ለዘመናዊ ትራንስፖርት አገልግሎት፣ ለጥቃቅንና አነስተኛ እንዲሁም ለስደተኞች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ይውላል።

ስምምነቱን የተፈራትረሙት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚንስትር አቶ አብዱልአዚዝ መሐመድና የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ካሮሊን ቱርክ ናቸው።
ሚንስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በብድር ከተገኘው 6 ነጥብ 51 ቢሊዮን ብሩ በከተሞች ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማስፋፋት ይውላል።
እንዲሁም 4 ነጥብ 34 ቢሊዮን ብር ለጥቃቅንና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ማጠናከሪያ እንደሚውልም ተናግረዋል።
የተገኘው ገንዘብ አገሪቱ በቀጣይ ትኩረት ሰጥታ የምትሰራባቸውን ዘርፎች በላቀ ሁኔታ ለማስቀጠል እንደሚረዳም አቶ አብዱልአዚዝ ተናግረዋል።
ባንኩ  ብድሩ አገሪቱ የነደፈችውን ሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ የሚያሳልጥና እድገቱን ለማስቀጠል እንደሚያግዝ ገልጸዋል።
ምንጭ፡- ኢዜአ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy