Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በሃገሪቱ የልማትና ኢንቨስትመንት ስራዎች ላይ ለመሳተፍ የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር ማነቆ ሆኖብናል – የዳያስፖራ አባላት

0 402

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በሃገራችን መጥተን በልማትና በኢንቨስትመንት ስራዎች ላይ ለመሳተፍ የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር ማነቆ ሆኖብናል ሲሉ የዳያስፖራ አባላት ተናገሩ።

የዳያስፖራ አባላቱ በአማራ ክልል ባሉ የኢንቨስትመንት ሁኔታ አማራጮችና የጥረት ኮርፖሬት እንቅስቃሴ ዙሪያ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር ተወያይተዋል።

በባህር ዳር ከተማ እየተከበረ ባለው የክልሉ የዳያስፖራ ቀን በዓል አከባበር ላይ እየተሳተፉ ያሉ አባላት፥ በሃገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች የሚያቀርቸቧውን የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ያለምክንያት ውድቅ የሚያደርጉና የሚያጓትቱ የመንግስት ስራ አስፈጻሚዎች እናንዳሉ ተናግረዋል።

መንግስት ቅድመ ሁኔታዎችን አመቻችቶ ሃገራቸው መጥተው እንዲያለሙ ጥሪ እንደሚያቀርብላቸው የጠቀሱት አባላቱ፥ በርካታ ኢትጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ይዘው እንደሚመጡ ይመጣሉ ብለዋል።

ይሁን እንጅ በመሬትትና መሬት ነክ ጉዳዮች በኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥና የግንባታ ስራ ላይ ችግር እንደሚገጥማቸው አንስተዋል።

አንዳንድ የኪራይ ሰብሳቢ አመለካከት ያላቸው የስራ አስፈጻሚ አካላት፥ ቀላል የማይባል ገንዘብ በይፋ ከመጠየቅ እስከ የመኖሪያ ቤትና ተሽከርካሪ እስከማስገዛት መድረሳቸውንም ያነሳሉ።

በዚህም ዳያስፖራው እቅዱን እንዳይፈጽምና ተሰላችቶ ወደ መጣበት እንዲመለስ እየሆነም ነው ያሉት።

በቀጣይ ይህ የሚፈታ ከሆነ ዳያስፖራው በትውልድ ሃገሩ ለማልማት ፍላጎት እንዳለውም በነበረው ውይይት ላይ ገልጸዋል።

የዳያስፖራ አባላቱ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ከሚመለከታቸው የመንግሰት አካላት ጋር የሚያደርጉት ውይይት ቀጥሎ እየተካሄደ ነው።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy