DEVELOPMENT

በባህር ዳር አለማቀፍ ስታዲየም በዲያስፖራውና በአመራሩ መካከል የተካሄደ የእግር ኳስ ጨዋታ የዲያስፖራው ቡድን 5ለ2 በማሸነፍ ተጠናቀቀ፡፡

By Admin

July 31, 2016

በባህር ዳር አለማቀፍ ስታዲየም በዲያስፖራውና በአመራሩ መካከል የተካሄደ የእግር ኳስ ጨዋታ የዲያስፖራው ቡድን 5ለ2 በማሸነፍ ተጠናቀቀ፡፡

በጨዋታው የተገኙት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር የተከበሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እንደገለፁት የስፖርት ዋና ዓላማው ወንድማማችነትን እና ቤተሰባዊነትን መፍጠር መቻል ነው፡፡

በዚህም የእግር ኳስ ጨዋታው በዲያስፖራው ማህበረሰብና በአመራሩ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ነው፡፡ ይህ ከሆነ በክልሉ ባሉት የልማት ስራዎች በጋራ በመሳተፍ ያለውን ፈጣን ዕድገት በማስቀጠል ዋነኛ ጠላታችን የሆነውን ድህነት ከመሠረቱ መናድ ያስችለናል ብለዋል፡፡