Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ሰላም ወዳዱ የመዲናዋ ነዋሪ የፀረ- ሰላም ሀይሎችን በሬ ወለደ ቅስቀሳ ወደ ኋላ በማለት መደበኛ ተግባሩን ሲያከናውን መዋሉን ፖሊስ ገለፀ

0 1,002

Get real time updates directly on you device, subscribe now.


ሰላም ወዳዱ የመዲናዋ ነዋሪ የፀረ- ሰላም ሀይሎችን በሬ ወለደ ቅስቀሳ ወደ ኋላ በማለት መደበኛ ተግባሩን ሲያከናውን መዋሉን ፖሊስ ገለፀ

ፀረ-ሰላም ሀይሎች የአዲስ አበባ ነዋሪ ሰልፍ እንዲወጣ ቢቀሰቅሱም ምንም አይነት ሰልፍ አለመደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ነዋሪው የፀረ- ሰላም ሀይሎችን በሬ ወለደ ቅስቀሳ ወደ ኋላ በማለት የእለት ከእለት ተግባሩን ሲያከናውን መዋሉን ኮሚሽኑ ገልፆ፥ በዛሬው እለት በመዲናችን የነበረው የፀጥታ ሁኔታ ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር ኮሚሽኑ ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ሰላም ወዳዱ ህዝባችን ከፖሊስ የተላለፈለትን መልእክት በመቀበል እና ተግባራዊ በማድረግ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም ጥቆማ በመስጠት እና አካባቢውን በመጠበቅ እያደረገ ላለው ትብብር ምስጋናውን አቅርቦ ትብብሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

በተጨማሪም ህዝቡ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥመው ለፀጥታ ኃይሉ ጥቆማ የመስጠት ልምዱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ኮሚሽኑ ጠይቋል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy