Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በሰሞኑ ሁከት ከቡራዩ አካባቢ ማንነትን መሰረት ባደረገ ጥቃት ለተፈናቀሉ ከ100 ለሚበልጡ ዜጎች ድጋፍ እየተደረገ ነው

0 395

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በሰሞኑ ሁከት ከቡራዩ አካባቢ ማንነትን መሰረት ባደረገ ጥቃት ለተፈናቀሉ ከ100 ለሚበልጡ ዜጎች ድጋፍ እየተደረገ ነው

በሰሞኑ ሁከት ከቡራዩ አካባቢ ማንነትን መሰረት ባደረገ ጥቃት ለተፈናቀሉ ከ100 ለሚበልጡ ዜጎች ድጋፍ እየተደረገ ነው

በኦሮሚያ ክልል ቡራዩ አካባቢ እየተንቀሳቀሱ ያሉ የሁከት ሃይሎች ባለፉት አራት ቀናት ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት አድርሰዋል።

እነዚህ ሃይሎች መኖሪያቸውን በስፍራው ባደረጉ ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት መፈጸማቸውን የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ዜጎች ተናግረዋል።

ጥቃቱ እስከተፈጸመበት እስካለፈው ሰኞ ድረስ፥ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ዜጎች በቡራዩ አካባቢ ከሶስት እስከ አስር አመት መኖራቸውን ይናገራሉ።

ባለፉት አራት ቀናት ግን አመታትን ከኖሩበት አካባቢ የሚያፈናቅል ንብረታቸውን ትቶ የሚያሸሽ ጥቃት ደረሰብን ይላሉ፥ በቡራዩ አካባቢ ልዩ ስፍራው ቤሩ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ዜጎች።

የጥቃቱ ሰለባዎች እንደሚሉት ድርጊቱ በጥቂት ሁከት እና ዘረፋን በሚሹ ሃይሎች ከመፈፀሙ በስተቀር፥ ከሌላው የቡራዩ ከተማ ነዋሪ የኦሮሞ ህዝብ የደረሰባቸው በደል እንደሌለም ገልጸዋል።

በጥቃቱ ምክንያት ይኖሩበት የነበረውን አካባቢ ለቀው ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል፥ 112 የሚሆኑት በአዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ በአንድ የቀበሌ ወጣቶች መዝናኛ ውስጥ በጊዜያዊነት ተጠልለው ይገኛሉ።

ለእነዚህ ዜጎች በአሁኑ ወቅት ተጠልለው በሚገኙበት አካባቢ የምግብ እና አልባሳት ድጋፍ እየተደረገ ነው።

 

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy