Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በኢትዮጵያ መንግስት እና በኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር መካከል የሰላም ስምምነት ተፈረመ

1 539

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር የኢፌዲሪን ሕገመንግስት በመጻረር የትጥቅ ትግልን አማራጭ አድርጎ ሲታገል ቆይቷል።

ግንባሩ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ከመንግስት ጋር የተለያዩ ውይይቶችን አድርጎ የትጥቅ ትግል አማራጩን በመተው በሰላማዊ መንገድ ለመታገልና ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በመቀበል ለመንቀሳቀስ እና ለኢትዮጵያ ሔራዊ ጥቅም ለመቆም መወሰኑን ገልጿል።

ስምንት ነጥቦች ያሉት የሰላም ስምምነትም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተፈራርሟል።

የመከላከያ ሚንስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ በትጥቅ ትግል ውስጥ የነበሩ የተለያዩ ድርጅቶችና ቡድኖች በሰላማዊ መንገድ እየገቡ መሆናቸውን ገልጸው የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባርም የዚሁ አካል ነው ብለዋል።

መንግስት የትጥቅ ትግል አማራጭን በመተው በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ የሚፈልጉ አካላትን ለመቀበል ሁሌም ዝግጁ መሆኑንም የመከላከያ ሚንስትሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር ሊቀመንበር አቶ ቱዋት ፖል ቻይ ከጦርነት ምንም የሚገኝ ነገር ስለሌለ ወደ ሰላማዊ አማራጭ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለሰላማዊ ትግል የተመቸ በመሆኑ አባሎቻቸውን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገሉም ገልጸዋል።

  1. dmarko says

    Hagerachinin betalak halafinet yizo leginbata meseretawi hunetawochin ewun yaderege keihadeg befit tarikun yawokut mengist beEthiopia tarik alneberem bil alisaSatm. Kezih mengist gar abro lehager yalasebe Arbegna, arbdgna aydelem

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy