Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኢትዮጵያ የሶማሊያን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት እንደምትሠራ ገለጸች

0 321

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኢትዮጵያ የሶማሊያን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት እንደምትሠራ ገለጸች

ህዳር 16፣2009

ኢትዮጵያ የሶማሊያን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ከሶማሊያና ከኢጋድ አባል ሀገራት ጋር በትብብር እንደምትሠራ ገለጸች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኦማር አብዱረሺድ አሊ ሼርማክን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው በሶማሊያ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡

ኢትዮጵያ በሶማሊያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት እያደረገችው ባለው ጥረትና  የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በሚጠናከርበት መንገድ ዙሪያ መክረዋል፡፡

በተጨማሪው በሶማሊያ እየተካሄደ ስላለው የምርጫ ሂደት፣ የፋይናንስና ሲቪል ሠርቪስ ጉዳዮች ሶማሊያ በምትጠናክርበት ሁኔታ ላይ ተነጋግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ሶማሊያ የምትፈልገውን ድጋፍ እንደምታደርግና የሶማሊያን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ከሶማሊያና ከኢጋድ አባል ሀገራት ጋር በትብብር እንደምትሠራ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ በቃል አቀባያቸው ተወልደ ሙሉጌታ በኩል ገልፀዋል፡፡

ሪፖርተር:-ሜሮን በረዳ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy