Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የትግራይ ክልል ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤ ሹመቶችን አጸደቀ

0 1,674

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የትግራይ ክልል ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤ ሹመቶችን አጸደቀ

ህዳር 26፣2009

የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ፡፡

ምክር ቤቱ በዚሁ አስቸኳይ ጉባኤው  የቢሮ ሃላፊዎችን ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም የክልሉ ዋና ኦዲተር አዲስ ሹመቶችን አጽድቋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባይ ወልዱ ለሹመት ያቀረቧቸው የስራ ሃላፊዎች ድርጅቱ የህዝብን ጥያቄ ለመመለስ ያካሄደውን ሰፊ ግምገማ መነሻ በማድረግ ነው ብለዋል፡፡

በዚህም መሰረት

1/ዶክተር ኢንጂነር ገብረ መስቀል ካህሳይ የትምህርት  ቢሮ  ሃላፊ፣

2/ ዶክተር ተስፋ ሚካኤል ገብረ ዮሐንስ የውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ፣

3/ዶክተር ሙሉጌታ ሃጎስ የቴክኒክ ትምህርትና ሙያ ስልጠና ቢሮ ሃላፊ ፣

4/ዶክተር የትምወርቅ ገብረመስቀል የሴቶች ጉዳይ ቢሮ ፣

5/ዶክተር አትንኩት መዝገቡ በግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ በተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ተጨማሪ የቢሮ ሃላፊ እና

6/ ዶክተር አብረሃ  ኪሮስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ወደ ቢሮ እንዲያድግ በማድረግ ሃላፊ ሆነዋል፡፡

በተጨማሪም ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሀጎስ የተሾሙ ሲሆን በምክትል ፕሬዝዳንትነት ደግሞ አቶ አማኑኤል አሰፋ እንዲሁም ለክልሉ ዋና ኦዲተር ዶክተር ረዳኢ በርሄ ሆነው ተሹመዋል፡፡

ከዚህም ሌላ  የውሃ ሀብት ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ ገብረ መስቀል ታረቀ ለክልሉ የጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ፣ አቶ ጎይቶም ይብራህ ለወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ቢሮ ፣ ዶክተር ገብረህይወት ገብረእግዚአብሔር ለትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል፡፡

ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ መፈጸማቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy