Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት በአዲስ አበባ ተከፈተ

0 1,258

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት በአዲስ አበባ ተከፈተ

የአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት በአዲስ አበባ ተከፈተ

የአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት በአዲስ አበባ ተከፍቷል።

ምክር ቤቱ የአሜሪካና የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንትና የንግድ ግንኙነት ለማጠናከር ያስችላል ተብሎለታል።

በኢትዮጵያና በአፍሪካ አገራት በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች በተሰማሩ የአሜሪካ ኩባንያዎች ትብብር የተቋቋመው ምክር ቤቱ የኩባንያዎቹ ባለቤቶች በንግድ ዘርፍ ያላቸውን ልምድ በመጠቀም የሎጅስቲክ ወጪ ለመቀነስና ለሥራ የሚያስፈልገውን የሠው ኃይል ለመመጠን የሚያስችል ምክክር እንዲያደርጉ ያግዛል ተብሏል።

የፋይናንስ ፍሰቱን በመረዳትና ከውጭ ምንዛሪ ጋር የተያያዙ ችግሮችን በመለየት ከመንግሥት ጋር በጋራ በመሆን ለችግሮቹ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚሠራም ነው የተጠቆመው።

የአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት በኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት አቶ ዳንኤል ኃይሉ እንዳሉት፥ ምክር ቤቱ በአሜሪካና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የኢንቨስትመንትና የንግድ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል።

በኢትዮጵያ ግልጽነትና ቀጣይነት ያለው የንግድና ኢንቨስትመንት ሥራ ባህል እንዲሆን እንደሚሠራና የኢንቨስትመንት ሥራዎች በምን መልኩ እንደሚተገበሩ ምክር ቤቱ ለአዳዲስ ኩባንያዎች ያስተዋውቃል ብለዋል።

ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ ልምድ ያላቸው ኩባንያዎች ልምዳቸውን አዲስ ለሚመጡ ኩባንያዎች የሚያስተላልፉበት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠርም ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy