Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ዶክተር ወርቅነህ ከዩኤስኤይድ ሀላፊ ጋይል ስሚዝ ጋር ተወያዩ

0 1,642

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ዶክተር ወርቅነህ ከዩኤስኤይድ ሀላፊ ጋይል ስሚዝ ጋር ተወያዩ

ዶክተር ወርቅነህ ከዩኤስኤይድ ሀላፊ ጋይል ስሚዝ ጋር ተወያዩ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ከዩናይትድ ስቴትስ የዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (ዩኤስኤይድ) ሀላፊ ጋይል ስሚዝ ጋር ተወያዩ።

በውይይታቸው ዩኤስኤይድ በኢትዮጵያ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ ዜጎች ውጤታማ እንዲሆኑ እና አቅማቸውን በመገንባት ረገድ እገዛ ሲያደርግ መቆየቱን ዶክተር ወርቅነህ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎች በሀገሪቱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች በንቃት እንዲሳተፉ ርብርብ እያደረገ መሆኑንም ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።

መንግስት የዜጎችን ፍላጎት በማሟላት የሀገሪቱን ህዳሴ ለማረጋገጥ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑንና ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን እያስፋፋ እንደሚገኝም ለአስተዳዳሪዋ ነግረዋቸዋል።

ኤጀንሲው ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ፣ በስራ ፈጠራ እንዲሁም በማህበረሰብ ልማት መስኮች ያለውን አጋርነት አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

ዶክተር ወርቅነህ በኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ላይም ለሀላፊዋ ገለፃ አድርገውላቸዋል።

ጋይል ስሚዝ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ መንግስት የሀገሪቱን ማህበረ ኢኮኖሚ እና ፖለቲካዊ እድገት ፍትሃዊ እና ቀጣይነት ያለው ለማድረግ ያከናወናቸውን ተግባራት አድንቀዋል።

ኤጀንሲው ኢትዮጵያ ድህነትን ለማጥፋት የምታደርገውን ጥረት እንደሚደግፍም ገልፀዋል።

 

ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy