Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት አጠናክራ ትቀጥላለች- ዶ/ር ወርቅነህ

0 631

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት አጠናክራ ትቀጥላለች- ዶ/ር ወርቅነህ

ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት አጠናክራ ትቀጥላለች- ዶ/ር ወርቅነህ

ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ተናገሩ።

ዶክተር ወርቅነህ ትናንት ምሽት መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የውጭ ሀገራት አምባሳደሮች፣ አለም አቀፍ ደርጅቶች እና ተቋማት ሃላፊዎች ጋር የትውውቅ ፕሮግራም አካሂደዋል።

ሚንስትሩ በዚሁ ጊዜም፥ በአሁኑ ወቅት መንግስት የንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፉን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሉም ተናግረዋል።

ሀገሪቱ የምታካሄደዉ የኢንደስትሪ ልማት ግንባታም ለዚህ ዘርፍ እደገት የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

የኢንደስትሪ ፓርኮች የውጭ ቀጥታ ኢንቭስተመንትን እየሳቡ እና ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል እየፈጠሩ መሆኑንም ዶክተር ወርቅነህ ተናግረዋል።

ዶከተር ወርቅነህ አምባሳደሮቹን እና የአለም አቀፍ ተቋሟት ሃላፊዎቹን ኢትዮጵያ የምታካሂደውን ሁሉን አቀፍ የልማት እንቅስቃሴ ለመደገፍ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረዉ አንዲቀጥሉ ጠየቀዋል።

ሚንስትሩ አያይዘውም፥ ኢትዮጵያ በአህጉራዊ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ሰላም እና መረጋጋት እንዲፈጠር የምታደርገዉን አስተዋፅኦም አጠናክራ ትቀጥላልች ብለዋል።

 

በስላባት ማናየ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy