Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

መንግስት ስልጣንን ያለአግባብ በተጠቀሙና በብልሹ አሰራር በተዘፈቁ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ገለፀ

0 629

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

መንግስት ስልጣንን ያለአግባብ በተጠቀሙና በብልሹ አሰራር በተዘፈቁ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ገለፀ

መንግስት ስልጣንን ያለአግባብ በተጠቀሙና በብልሹ አሰራር በተዘፈቁ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ገለፀ

ስልጣንን አለአግባብ በተጠቀሙና በብልሹ አሰራር በተዘፈቁ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለፁ።

በሃገሪቱ የተከሰተውን ሁከት ለማስቆም ተግባራዊ የሆነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ላይ ምንም አይነት ተፅእኖ እንዳላሳደረም ተናግረዋል።

በኢህአዴግ ምክር ቤትና ስራ አስፈፃሚው በህዝቡ ዘንድ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታትና ስልጣንን ያለአግባብ የመጠቀም ዝንባሌን ለማስወገድ የተቀመጠው በጥልቀት የመታደስ አቅጣጫ በመግባባትና በጥሩ መንፈስ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የጠቆሙት።

እስካሁን የተወሰዱት እርምጃዎች ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ መሆናቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ስልጣናቸውን አላግባብ በተጠቀሙና በብልሹ አሰራር በተዘፈቁ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ተግባር እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የተከሰተውን ሁከት ለማስቆም ተግባራዊ የተደረገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሃገሪቱን ወደ ቀድሞ ሰላሟ መመለሱንና ለውጤቱ መገኘትም የህዝቡ ሚና ከፍተኛ እንደነበር ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት።

በክልሎች እና ወደ ታች ባሉ የመንግስት መዋቅሮች በአዲስ መልክ የማደራጀት ስራው በተገቢው መንገድ እየተከናወነ እንደሆነም ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ11ኛው የብሄሮች፣ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን አደረሳችሁ የሚል መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፥ የተዛቡ አመለካከቶችን ወደ ጎን በመተው አገራዊ አንድነትን የበለጠ ማጎልበት እንደሚገባ ገልፀዋል።

ብሄሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የተጀመረውን የህዳሴ ጉዞ በአንድነት በማስቀጠል አገሪቱን ወደ ተሻለ ምእራፍ ማሸጋገር ይገባል ብለዋል።

የብሄሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ጠንካራ ኢትዮጵያዊ አንድነት የተፈጠረበት፣ በአገሪቱ የነበሩ የተዛቡ አመለካከቶች የተወገዱበትና አንድ የኢኮኖሚና ፖለቲካ ማሕበረሰብ ለመፍጠር መሰረት የተጣለበት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

በዓሉ አገራዊ አንድነትን የበለጠ የሚጎለብትበት እንዲሁም ሕብረ ብሔራዊነት የሚጠናከርበት ነውም ብለዋል።

 

 

ምንጭ፦ ኢብኮ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy