Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

አንቶኒዮ ጉተሬዝ የኢትዮጵያን ሰላም የማስፈንና ስደተኞችን የማስተናገድ ጥረት አደነቁ

0 366

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ሠላምና መረጋጋት በማስፈንና ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ ረገድ የምታደርገውን ጥረት አደነቁ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በ28ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ከገቡት አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ምክክር አካሂደዋል።

ዋና ጸሃፊው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ሰላሟ የተጠበቀ ሃገር መሆኗ በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ተስፋ የሚሰጥ ነው።

በሶማሊያና ደቡብ ሱዳን እንዲሁም በኢጋድና በሌሎች የአህጉሪቱ አካባቢዎች ሠላም ለማስፈን ኢትዮጵያ እያደረገች ያለውን ጥረትም አድንቀዋል።

የሃገሪቱን ሰላም ዋስትና አድርገው ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡትን የጎረቤት ሃገራት ስደተኞች ተቀብላ በማስተናገድ ረገድም የምታደርገው ሰብዓዊ ተግባር የሚመሰገን መሆኑንም ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው፥ በቀጠናውም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍንና ልማት እንዲረጋገጥ ከመንግስታቱ ድርጅታ ጋር ኢትዮጵያ በቅርበት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።

ዋና ጸሃፊውም እነዚህንና ሌሎች ኢትዮጵያ የምታከናውናቸው ተግባራት የመንግስታቱ ድርጅት ድጋፍ እንደማይለያት አረጋግጠዋል።

በኅብረቱ ጉባዔ አጀንዳዎችና ሌሎች አህጉራዊ ጉዳዮች ዙሪያም በስፋት ምክክር አካሂደዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በአዲስ አበባ በሚካሄደው 28ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ የክብር ተጋባዥ መሆናቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።

FBC

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy