Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ሀገሪቱ የምትከተለውን ስርዓት መረዳት ለተሻለ የመገናኛ ብዙሃን ስራ መሰረት ነው – ዶ/ር ደብረፂዮን

0 497

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ሀገሪቱ የምትከተለውን ስርዓት ከምትመራበት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ጋር አጣምሮ ማወቅ ለተሻለ የመገናኛ ብዙሃን ስራ መሰረት መሆኑን የመገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ደብረፂዮን ገብረሚካኤል ተናግረዋል።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በአጠቃላይ ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ነው ሚኒስትሩ ይህን ያሉት።

ዶክተር ደብረፂዮን “ኢትዮጵያ ለምን የልማታዊ ዴሞክራሲ መስመርን መከተል ወደድች” በሚል ርእስ በመድረኩ ላይ ለተገኙ ጋዜጠኞች የውይይት መነሻ ሃሳብ አቅርበዋል።

በመነሻ ጽሁፉም ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የተሻለ አማራጭ ያደረገችው የልማታዊ መስመር ላይ ዴሞክራሲን ጨምራበት በዚሁ መስመር መመራትን ነው ብለዋል።

ይሄኛውን መንገድ የሚከተል መንግስት ሶስት ባህርያትን የተላበሰ ነው ሲሉም ዶክተር ደብረፂዮን አብራርተዋል።

እነዚህም ልማትን ህልውና አድርጎ መውሰድ፣ ከባለሀብቱ ጋር የተነጻጸረ ኢኮኖሚያዊ ነፃነት እንዲኖር ማድረግ እና ልማታዊ አስተሳሰብ የበላይነት እንዲኖረው ማስቻል ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግስትም በሶስቱ የልማታዊ መንግስታት ባህሪ ሲለካ፥ ዜጎች መላ ትኩረታቸው ልማት ከሆነ 14 ዓመታት መቆጠሩን ነው በማሳያነት ያቀረቡት።

በተመረጠ እና በተጠና መንገድ የገበያ ጉድለትን የመሙላት ነፃነት የሰጠ ሰርዓትን የሚከተለው መንግስት የሚያስተዳድረው የበዛ ሀብት፣ ባለስልጣናቱም የሚያዙበት ገንዘብ አለው፤ ከዚህ የመነጩት ፈተናዎችም አሉበት ብለዋል።

ሚኒስትሩ አያይዘውም ደቡብ ኮርያውያን ከተመፅዋችነት ወጥተው ሀገራትን በቋሚነት እስከመደገፍ የደረሱት የልማታዊ አስተሳሰብ የበላይነትን ማምጣት የቻሉ መገናኛ ብዙሃን ስለነበራቸው መሆኑን ጠቁመዋል።

ዶክተር ደብረፂዮን በመድረኩ ላይ ለተሳተፉ አካላት ኢትዮጵያ ህዝብን ከድህነት ለማውጣት የሚተጋ መገናኛ ብዙሃን ያሻታል ብለዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy