Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የ‹‹ሰማያዊ›› የም/ቤት ሰብሳቢ፣ ህዝብን በማነሳሳት ተከሰሱ

0 467

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የ‹‹ሰማያዊ›› ፓርቲ ብሄራዊ ም/ቤት ሰብሳቢ አቶ ይድነቃቸው ከበደ፣ የሀሳብ ወሬዎችን በማውራት፣ ሕዝብን በማነሳሳት ወንጀል የተከሰሱ ሲሆን ከፍ/ቤት በዋስ ተለቀዋል፡፡
በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ከትናንት በስቲያ ክሳቸው የተነበበው አቶ ይድነቃቸው፤ ጳጉሜ 13 ቀን 2008 ዓ.ም በግምት ከቀኑ በ3 ሰዓት፣ በአቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 9፣ ልዩ ቦታው ቂሎንጦ ማረሚያ ቤት አካባቢ፣ የህግ ታራሚ ቤተሰቦችን መንግስት ታራሚዎችን አቃጥሎ ለምን ዝም ብላችሁ ታያላችሁ? አትጮሁም ወይ፤ አታለቅሱም ወይ?! አሁን እኛም መታገል አለብን›› በማለት የቀሰቀሰ በመሆኑ በፈፀመው የሀሰት ወሬዎችን በማውራት ህዝብን የማነሳሳት ወንጀል ተከሷል ይላል፡፡
ተከሳሹም በክሱ ላይ ያላቸውን መቃወሚያ ይዘው እንዲቀርቡ ለየካቲት 9 ቀን 2009 የተቀጠሩ ሲሆን ቀደም ሲል በዚሁ ጉዳይ ከፖሊስ ጣቢያ የ5000 ሺ ብር ዋስ አስይዘው የተለቀቁ ሲሆን ከፍ/ቤትም በ1500 ብር ዋስ ተለቀዋል፡፡

AddisAdmass

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy