Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በሻሸመኔ ቤት ተከራይተው ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር ሲልኩ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

0 420

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በሻሸመኔ ከተማ የመኖሪያ ቤት በመከራየት ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር ሲልኩ የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

ግለሰቦቹ በሻሸመኔ ከተማ አዋሾ ክፍለ ከተማ 01 ቀበሌ የተከራዩትን ቤት የጫት መቃሚያ በማስመሰል ህገ-ወጥ ተግባር ሲፈፅሙ ነበር ተብሏል ፡፡

የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የወረዳ ሁለት ፖሊስ ፅህፈት ቤት ከነዋሪዎች ከደረሰው ጥቆማ በመነሳት ባደረገው ኦፕሬሽን፥ ሁለት ተጠርጣሪዎችን ፣ 47 ፓስፖርቶችን፣ የህክምና ማስረጃዎችን ፣ ፎቶዎችን እና የሺሻ እቃዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት ሁለት ግለሰቦች ሌላ ሁለት ያመለጡ ሲሆን ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል የተጠናከረ ጥረት እየተደረገ መሆኑን፥ የፅህፈት ቤቱ የአካባቢ ፀጥታና የወንጀል መከላከል የስራ ሂደት ረዳት ሳጅን ሙህዲን ማህመድ ገልፀዋል፡፡

በህገወጥ መንገድ የተላኩ ሰዎች አሉ የሚል ጥቆማ ስለደረሰንም ምርመራችንን አጠናክረን ቀጥለናል ብለዋል ረዳት ሳጅን ሙህዲን፡፡ FBC

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy