Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በአነስተኛ አርሶና አርብቶ አደሮች ሀብት

0 1,348

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በአነስተኛ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች እጅ ሃብት እየተፈጠረ መሄዱ ሀገሪቱ የነገ መዳረሻዋ ኢንዱስትሪ ለመሆኑ ማሳያ ነው አለ የመንግስት ኮሙኒዩኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት።

ጽህፈት ቤቱ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት በላከው ሳምንታዊ መግለጫ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂን ውጤታማነት ከሚመሰክሩ መካከል በየዓመቱ ምርትና ምርታማነታቸውን እያሳደጉ ወደ ባለሃብትነት የሚሸጋገሩ እነኚህ የልማት ጀግኖቻችን ናቸው ብሏል።

ስምንተኛው ሀገር አቀፍ የአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በዓል ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት በደማቅ ስነሥርዓት በመከበር ላይ መሆኑም ብቁና ተወዳዳሪ አርሶ አደሮችንና ከፊል አርብቶ አደሮችን በማበረታታት ወደ ኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ እንዲሸጋገሩ ማትጋት ነው ብሏል ጽህፈት ቤቱ በመግለጫው፡፡

ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል ወይም ጥሪት ያፈሩ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ወደ ባለሃብትነት የሚሸጋገሩበት ዕለት በመሆኑም በዓሉ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ነው።

የኢፌዴሪ መንግሥት ለመላው አርሶ አደሮች እና ከፊል አርብቶ አደሮች እንዲሁም በስራ ትጋታቸው ተሸላሚ ለሚሆኑት ለበዓሉ እንኳን አደረሳችሁ ብሏል።

ሁሉም ባለድርሻ አካላትም ወደ ኢንዱስትሪ ልማት የሚደረገውን ሽግግር ለማሳካት ጥረቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጽህፈት ቤቱ ጥሪውን አቅርቧል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy