Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በአዲስ አበባ ቆሼ አካባቢ በደረሰ የቆሻሻ ተደርምሶ እስካሁን የ46 ሰዎች ህይወት አለፈ

0 696

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በአዲስ አበባ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የተከመረ ቆሻሻ ተደርምሶ እስካሁን የ46 ሰዎች ህይወት አለፈ።

ማምሻውን የአዲስ አበባ ከንቲባ ድሪባ ኩማ በሰጡት መግለጫ የሟቾቹ ቁጥር ወደ 46 ከፍ ብሏል።

ከሟቾቹ ውስጥ 32 ሴቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ ወንዶች መሆናቸውንም ከንቲባው ገልጸዋል።

አሁን ላይ አደጋውን የመቀነስ እና ህይዎት የማዳን ስራው እንደቀጠለ ነው ብለዋል።

ተጨማሪ ጉዳት እንዳይደርስም በአካባቢው የሚገኙትን ነዋሪዎች ራቅ ወዳለ ቦታ የማስፈር ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ጉዳቱ ለደረሰባቸው ነዋሪዎችም የሰብዓዊና የተለያዩ ድጋፎች እየተደረገ ነው ያሉት ከንቲባው፥ ከተማ አስተዳደሩ ኮሚቴዎችን በማቋቋም ህይዎት የማዳኑንና የተጎዱትን የማቋቋም ስራ ከተለያዩ አካላት ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ተከምሮ የነበረው ቆሻሻ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በአካባቢው በሚገኙ ቤቶች ላይ ተደርምሶ ጉዳት አድርሷል።

አደጋው ከሟቾች በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት አድርሷል።

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎችም በአለርት ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy