Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በአድዋ ድል ለሁሉም ተምሣሌት የሆነ ተግባር ነው፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

0 744

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኢትዮጵያ ከ121 አመታት በፊት ጭቆና እና የሰው ልጆች ሰብአዊ መብት ጥሰትን በመቃወም በአድዋ ላይ ያደረገችው ተጋድሎ ለሁሉም ተምሣሌት የሆነ ተግባር መሆኑን የኢፌድሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሂሩት ዘመነ ገለፁ፡፡የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት 34ተኛውን መደበኛ ጉባኤ በጄኔቫ እያካሄደ ነው፡፡የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤቱ የ19 ሃገራትንና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሰብአዊ መብት አያያዝ እና አጠባበቅ ሪፖርትን አድምጧል፡፡ሚኒስትር ዴኤታዋ ወይዘሮ ሂሩት በኢትዮጵያ ባለፉት 25 አመታት  በድህነት ቅነሣ፣ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እመርታ እና በዜጐች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መብቶች ዙሪያ ያከናወነችውን ስራዎች አብራርተዋል ለምክር ቤቱ፡፡ነገር ግን ሃገሪቱ እያስመዘገበችው ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በተለያዩ መሰናክሎች እየተፈተነ መሆኑን ነው የገለፁት፡፡ባለፉት ወራት በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ህጋዊ ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎችን ሽፋን በማድረግ በፀረ-ሰላም ሃይሎች የተነሳውን ሁከትና ብጥብጥ ለአብነት በማንሳት፡፡በወቅቱ ተነስቶ በነበረው ሁከት እና ግርግር የጠፋውን የሰው ህይወት በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እያደረገ ስላለው ምርመራ አብራርተዋል ለምክር ቤቱ፡፡ኮሚሽኑ ሁኔታውን አጣርቶ በቅርብ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግም ወይዘሮ ሂሩት ተናግረዋል፡፡በ34ተኛው የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ምክር ቤት ጉባኤ ከ1ዐ7 በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡ዘገባውን ያደረሰን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ነው፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy