Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በኢንዱስትሪ ፓርኮች አቅራቢያ የደረቅ ወደቦች ግንባታ ሊካሄድ ነው

0 1,553

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በኢንዱስትሪ የሚመረቱ ምርቶችን በፍጥነት ወደ ውጪ ለመላክ እንዲቻል በኢንዱስትሪ ፓርኮች አቅራቢያ የደረቅ ወደቦች ግንባታ ሥራን የማስፋፋት ተግባር እንደሚያከናውን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ገለጸ።ደርጅቱ ለመገናኛ ብዙሃንና ለፌዴራል ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የባቦጋያ ማሪታይም ማሰልጠኛ፣ የሞጆና የገላን ደረቅ ወደቦች ተርሚናሎችን ያሉበትን ሁኔታ አስጎብኝቷል።የድርጅቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ገብረሕይወት እንደተናገሩት፤ ያሉትን ሰባት የደረቅ ወደቦች ከማስፋፋት ጎን ለጎን በኢንዱስትሪ ፓርኮች አካባቢም ደረቅ ወደቦች ይገነባሉ።

እንደ አቶ ደሳለኝ ገለጻ፤ ድርጅቱ በሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ አቅራቢያ የደረቅ ወደብ ለመገንባት ዝግጅት እየተደረገ ነው። በአማራ ክልል በወረታ ከተማ ሌላ የደረቅ ወደብ ለመገንባት የጥናት ሥራ እየተካሄደ ይገኛል።የደረቅ ወደቦች ግንባታ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚወጡ ምርቶችን በፍጥነት ወደ ውጪ ለመላክ እንደሚያስችሉ ምክትል ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

የድርጅቱ ተጠባባቂ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ተፈራ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ከውጪ ወደ አገር ውስጥ ከሚገቡ ኮንቴነሮች መካከል 80 በመቶውን የሚይዘው የሞጆ የደረቅ ወደብ ተርሚናል ነው። ለዚህ ተርሚናል የበለጠ አቅም ለመፍጠር በሚያስችል መልኩ የማስፋፊያ ስራ እየተከናወነለት ይገኛል።የደረቅ ወደቡ ማስፋፊያ የሚከናወነው አሁን ካለው የ60 ሄክታር መሬት ስፋት ወደ 140 ሄክታር ለማድረስ መሆኑን ነው አቶ መስፍን ያስረዱት።ከጅቡቲ የሚጫኑ ኮንቴነሮችን በባቡር በማጓጓዝ ለማራገፍ የሚያስችል በስድስት ሄክታር ላይ ያረፈ የባቡር ሐዲድ ግንባታም እየተፋጠነ መሆኑን ነው የገለጹት።ለሚራገፉ ዕቃዎች ማቆያ የሚሆኑ ሁለት ትላልቅ መጋዘኖች  እየተሰሩ ሲሆን፤ በቀጣይም ሁለት እንደሚገነቡ ገልጸዋል። ምንጭ፡- ኢዜአ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy