Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ቻይና የአፍሪካን የኢንዱስትሪና ግብርና ዘርፎች ለማዘመን ድጋፍ እንደምታደርግ አስታወቀች

0 400

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ቻይና የአፍሪካ ሀገራት የኢንዱስትሪ እና የግብርና ዘርፎች እድገት እንዲፋጠኑ እና ዘመናዊ እንዲሆኑ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኗን አስታወቁ፡፡

ቻይና ለአፍሪካ ሀገራት መሪዎች 60 ቢለየን የአሜሪካ ዶላር በአህጉሪቱ መዋዕለንዋይ ለማፍሰስ በገባችው ቃል መሰረት ግማሽ ያህሉን ተግባራዊ ያደረገች መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሀገሪቱ ለአህጉሩ ሀገራት ከገባቸው የገንዘብ መጠን እሰካሁን ገሚሱን በኢንዱስትሪ እና መሰረተ ልማት ግንባታዎች ዘርፎች ልማት እንዳዋለች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ቻይና በአፍሪካ ሞባሳ ናይሮቢ የባቡር መስመር ግንባታ እና በሂደት ላይ ያለው የታንዛኒያ ወደብ ግንባታ ለአህጉሪቱ እያደረገች ካለችው ድጋፎች መካከል ከፊሎቹ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የቻይና ለአፍሪካ ልማት ፈንድ 5 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የነበረውን የካፒታል መጠን ወደ 10 ቢለየን የአሜሪካ ዶላር አሳድጓል ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ ዴይሊ ኒውስ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy