Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ኢትዮጵያን የአፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ እየሰራ መሆኑ መንግስት ተገለጸ

0 709

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ኢትዮጵያን የአፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ የተቀመጠውን ራዕይ እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪያል ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡የኮርፕሬሽኑ ሊቀመንበር ዶ/ር አርከበ እቁባይ እንደገለጹት አገሪቱን የአፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ የኢነርጂና የትራንስፖርት ዘርፎች ትኩረት ተሰጥቷቸዋል፡፡

እ.አ.አ ከ1992 ዓ.ም ጀምሮ የሀገሪቱ ምጣኔ ሃብት ፍጥነት እያደገ በመምጣቱ ባለፉት 13 አመታት ውስጥ ጠቅላላ አገራዊ ምርቱ በ11 በመቶ እየጨመረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡በዚህም ሀገሪቱ ከግብርና ወደ ኢንደስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋገር እየሰራች መሆኗን ገልጸዋል፡፡

መንግስትም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ፤ የሀገሪቱን ምጣኔ ማሳደግ፤ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ እድልን መፍጠርና የወጪ ንግድ መጠንን ማሳደግ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ነው የገለጹት፡፡የኢንደስትሪ ፓርኮቹ ለሀገሪቱ 100 ቢሊዮን ዶላር ያህል ገቢ ያስገኛሉ ተብሎ ይገመታል፡፡ምንጭ፡- ብሉምበርግ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy