Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ ነዋሪዎች ከቆሼ አካባቢ እንዲነሱ እየተደረገ ነው

0 409

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቆሼ አካባቢ ነዋሪዎችን ወደ ሌላ አካባቢ የማዛወር ስራ እየሰራ መሆኑን ከንቲባ ድሪባ ኩማ ተናገሩ።በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከትናንት በስቲያ ምሽት የቆሻሻ ክምር በመናዱ በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ይታወሳል።በቆሻሻ ክምር መናድ ምክንያት እስካሁን የ46 ሰዎች ህይወት ማለፉ ሲገለጽ በርካቶች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በወቅቱም የከተማ አስተዳደሩ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች፣ ፖሊስና የአካባቢው ኅብረተሰብ ባደረጉት ርብርብ የበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችን ሕይወት መታደግ ተችሏል።የአደጋውን መጠን የመቀነስ ስራም ተሰርቷል።

የአደጋው መጠን አሁንም ሊጨምር ይችላል ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ድሪባ ኩማ የአካባቢው ነዋሪዎችን የአደጋ ተጋላጭነት መቀነስ የሚያስችል ስራ ይሰራል ብለዋል።

የቆሻሻ መናድ አደጋ ከደረሰባቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በተጨማሪ ሌሎች የአደጋ ተጋላጭ ነዋሪዎችን ወደ ሌላ ቦታ ለማዛወር እየተሰራ መሆኑን ከንቲባ ድሪባ ኩማ ተናግረዋል።የአደጋው ተጎጂዎች ህክምና እየተከታተሉ ሲሆን ህይወታቸውን ያጡ ወገኖች የቀብር ስነ-ስርዓትም ዛሬ ከሰዓት እንደሚፈጸም ይጠበቃል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy