Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የየካቲት አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ጭማሪ አሳየ

0 500

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የየካቲት አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ጭማሪ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

ኤጀንሲው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ የተያዘው ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ ሰባት ነጥብ ዜሮ በመቶ ሆኗል።

የጥር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ስድስት ነጥብ አንድ በመቶ እንደነበር ያስታወሰው መግለጫው፤በየካቲት በዜሮ ነጥብ ስምንት በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን አመልክቷል።በተያዘው ወር ከምግብ ክፍሎች አኳያ ከሩዝ በስተቀር በእህል ዋጋ ላይ ቅናሽ የታየ ሲሆን፤ በተለይም በቃሪያና ጎመን፣ በጥራጥሬ ፣በድንች በቆጮና ቡና ዋጋ ላይ ጭማሪ በመታየቱ የዋጋ ግሽበቱ ከፍ እንዲል ምክንያት መሆኑን አመልክቷል፡፡

የዚህ ዓመት የየካቲት ወር ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የስድስት ነጥብ ሁለት በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንም አስታውሷል፡፡

ለዚህ ዋና ምክንያቶቹ በጫት፣ በልብስና በማገዶ እንጨት፣ በነዳጅ፣ በቤት እቃዎችና በቤት ማስጌጫዎች ላይ ጭማሪ በመታየቱ መሆኑን አመልክቷል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy