Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የፋይናንስ እጥረትና የዲዛይን ችግሮች ቤት ፈላጊዎች በጊዜ እና በጥራት ቤት እንዳያገኙ ምክንያት ሆነዋል ተባለ

0 364

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ቤት ፈላጊዎችን በጊዜ እና በጥራት ቤት እንዳያገኙ ማድረጉን የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ጥናት አመላከተ፡፡ጥናቱ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤቱ በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በ18 ወራት ውስጥ 50 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ቢያቅድም፥ ግንባታውን ብቻውን በማከናወኑ ቁጥራቸው 900 ሺህ የሚደርሱ ቤት ፈላጊዎችን ጥያቄ አሟልቶ መመለስ እንዳልቻለ አሳይቷል።

የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤትና ቤቶች ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ የጥናት ግኝቶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ምክክር አድርጓል።

በምክክሩ ላይ በቀረበው ጥናት በግዥ፣ በኮንትራት ውል እና በግብዓት አቅርቦት ላይ የተቀናጀ መረጃ እና ግልፅነት አለመኖሩ ተመላክቷል፡፡

የተቋማቱ አመራሮች እና ፈጻሚዎችም በስብሰባ አብዛኛውን ጊዜ ማሳለፍ አገልግሎቱ ላይ ችግር የፈጠረ ሌላው ግኝት ነው፡፡

የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት መሬት ተረክቦ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ሲገነባ፥ በቂ ገንዘብ ያለመመደብ እና የመሰረተ ልማት አውታሮች አለመሟላት በእቅዱ ዙሪያም ሳይመክር ወደ ሥራ የመግባት ችግርም በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡የቤቶች ግንባታ ቅድመ ጥናት አለማድረግ፣ የዲዛይን ችግሮችና የግብዓት እጥረቶችም ሌሎች በጫና ፈጣሪነት የተጠቀሱ ናቸአው፡፡

ለአብነትም በጀሞ ሳይት የብሎክ 220 ህንጻ የመዝመሙ ምክንያት የቅድመ አፈር ጥናት አለመከናወኑ ሲሆን ይህ ደግሞ ነዋሪዎችን ለእንግልት እና ለተጨማሪ ወጪ ዳርጓቸዋል፡፡

ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው ህንጻዎች ተገንብተው ወደ ህብረተሰቡ ከተላለፉ በኋላ ክትትል እንደማይደረግባቸው አንስተው፥ የመፀዳጃ ቤት ቱቦዎች መፈንዳት፣ የመሰረተልማት ሥራዎች በተለይም የውሃና የመብራት ችግሮች ይስተዋላሉ ነው ያሉት፡፡

ለፕሮጀክት ፅህፈት ቤቱ ሰራተኞች የፀደቀው ጥቅማጥቅም ባለመተግበሩ ምክንያት፥ በ2008 ዓ.ም ብቻ ከ2 ሺህ 280 ሰራተኞች መካከል 645ቱ ሥራቸውን የለቀቁ ሲሆን ይህም በቤቶች ግንባታ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡

ዘጠኝ ተቋራጮችም ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ጥፋታቸው ሳይገለፅላቸው መሰናበታቸውም አላግባብ መሆኑ በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡

ምክትል ዋና እንባ ጠባቂዋ ወይዘሮ ሰራዊት ስለሽ ከህግ ክፍተት ጋር በተያየዘ ለተነሱ ችግሮች፥ የወጡ አዋጆችን ማስፈፅሚያ ደንቦችን በማውጣት ሥራዎችን ሙሉ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል፡የህብረተሰቡን የቤት ፍላጎት ለማሟላትም ሌሎች አማራጮች ቢፈለጉ የሚል ጥቆማን አቅርበዋል ምክትል ዋና እንባ ጠባቂዋ፡፡

 

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy