Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ሂትለር ሚሊዮኖችን ያስገደሉበት ስልክ 195 ሺህ ፓውንድ ተሸጠ

0 291

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የናዚው መሪ አዶልፍ ሂትለር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈውበታል የተባለው ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ በአሜሪካ ሜሪላንድ ውስጥ በተካሄደ ጨረታ 195 ሺህ ፓውንድ መሸጡ ተዘግቧል፡፡
የሂትለር የጥፋት ሞባይል ተብሎ የሚጠራውና ከ70 አመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው የተነገረለት ይሄው ቀይ ቀለም ያለው ስልክ፣ በስተጀርባው የሂትለር ስም፣ የንስር ምስል እና የስዋስቲካ ምክልት እንዳለበት የዘገበው ቢቢሲ፣ ስሙ ያልተገለጸ ተጫራች በስልክ ባቀረበው የመወዳደሪያ ዋጋ አሸንፎ እንደገዛው ገልጧል፡፡
ብርጋዴር ጄኔራል ራልፍ ራይነር የተባሉ እንግሊዛዊ የጦር መሪ እ.ኤ.አ በ1945 በርሊን ውስጥ የሚገኘውን የሂትለር ምሽግ በጎበኙበት ወቅት፣ ይሄው ታሪካዊ ስልክ ከሩስያ የጦር መኮንኖች በስጦታ መልክ እንደተበረከተላቸውም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy