Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በምስራቅ ሸዋ ዞን 587 ካርቶን ሺሻ በድብቅ ሲጓጓዝ ተያዘ

0 3,667

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በምስራቅ ሸዋ ዞን ከፈንታሌ ወረዳ ወደ አዳማ ከተማ በድብቅ ሲጓጓዝ የነበረ 587 ካርቶን ሺሻ መያዙን ፖሊስ አስታወቀ።እቃው ሊያዝ የቻለው በአሸዋ ስር ተጭኖ ሲጓዝ የነበረበት ሲኖትራክ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው።

የዞኑ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ዓለሙ እንደገለፁት ኮድ 3 ኢት 77657 ሲኖትራክ ተሽከርካሪ የተገለበጠው ትናንት ከቀኑ 7 ሰዓት አሸዋ ጭኖ ከፈንታሌ ወረዳ መተሀራ ከተማ አካባቢ ወደ አዳማ ሲጓዝ ነው።

የፊት ጎማው ፈንድቶ ልዩ ስሙ አዴቻ በተባለው ስፍራ የመገልበጥ አደጋ ባጋጠመው ተሽከርካሪ ውስጥ አሸዋ ለብሶ በድብቅ ተጭኖ የነበረና 1ነጥብ አራት ሚሊዮን ብር ግምት ያለው 587 ካርቶን  ሺሻ በመዘርገፉ ሊያዝ ችሏል።የመኪናው አሽከርካሪና የህገ-ወጥ ዕቃው ባለቤት ለጊዜው በመሰወራቸው ፖሊስ ክትትል እያደረገ መሆኑንም ምክትል ኮማንደሩ ተናግረዋል ።

በአሳቻ የማጭበርበሪያ ዘዴዎች የሚካሄደው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ጉዳቱ ከፍተኛ ስለሆነ ህብረሰተቡ አካባቢውን በንቃት በመከታተልና ወንጀለኞችን ለፖሊስ በመጠቆም እንዲተባበር ምክትል ኮማንደር አስቻለው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy