Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ከህዳሴው ግድብ ሩጫ ተሳታፊዎች 21.7 ሚሊዮን ብር ተገኘ

0 417

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ባለፈው እሁድ በመላው አገሪቱ በተካሄደው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ሩጫ 21 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ከቲሸርት ሽያጭ መገኘቱን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባባሪያ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የቀረበው ቲሸርት ከተሳታፊዎች ያነሰ በመሆኑ አብዛኞቹ ያለቲሸርት መሳተፋቸውን ጽህፈት ቤቱ ገልጿል፡፡

በውድድሩ አዲስ አበባ 77 ሺህ፣ ኦሮሚያ 210 ሺህ እንዲሁም ትግራይ 50 ሺህ ተሳታፊዎችን ማስተናገዳቸው ታውቋል፡፡ የሌሎች ክልሎች የተጠቃለለ መረጃ አልደረሰም፡፡

በመሆኑም በሳምንቱ ከቲሸርት እና ከቦንድ ሽያጭ የተሰበሰበው ገንዘብ 44 ሚሊዮን ብር ደርሷል፡፡

የህዳሴው ግድብ የገቢ ማሰባሰቢያ ፐሮግራም በእግር ኳስ ጨዋታዎችም የሚቀጥል ሲሆን ከመጋቢት 14 እስከ 16 የሚካሄድ ይሆናል፡፡

ልዩ የቦንድ ሽያጭ ሳምንቱ ነገ የሚጠናቀቅ ሲሆን በክልሎች ጥያቄ ሊራዘም እንደሚችል ታውቋል፡፡

አዝመራው ሞሴ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy