Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ከአዲስ አበባ ካርቱም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

0 1,279

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

ከአዲስ አበባ ሱዳን ካርቱም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ዛሬ ተጀምሯል።

አገልግሎቱ በሙከራ ደረጃ የተጀመረ ሲሆን፥ የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች ግንኙነት ከማጎልበት አኳያ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን፥ የትራንስፖርት ባለስልጣን ገልጿል።

በባለስልጣኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ብቃት ማረጋገጫ ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ በላቸው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት፥ የአገልግሎቱ መጀመር በካርቱም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችና በመካካለኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የሁለቱም ሀገራት ዜጎች አማራጭ የመገናኛ ዘዴ ይሆናል።

ለኢንቨስትመንትና ቱሪዝም እድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

አገልግሎቱን ለማስጀመርም ከኢትዮጵያ በኩል አባይ፣ ኢትዮ ባስ፣ ጎልደንና የሰላም ልዩ አውቶብሶች ተመርጠዋል።

የአንድ ጉዞ ዋጋም 60 የአሜሪካ ዶላር ሲሆን፥ ከኢትዮጵያ በኩል ለሚቆረጥ ትኬት በእለቱ የምንዛሬ ተመን መሰረት በኢትዮጵያ ብር መቁረጥ ይቻላል።

ከአዲስ አበባ የሚነሱት አውቶብሶችም መነሻቸው መስቀል አደባባይ መሆኑን አቶ ተስፋዬ ጠቁመዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy