Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የመለስ ፋውንዴሽንና የአርብቶ አደሮች ፎረም የአርብቶ አደሮችን አቅም ለመገንባት ተስማሙ

0 332

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በአርብቶ አደር አካባቢ የሚኖሩ ሴቶችን እና ህፃናትን ለማስተማር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማስተዋወቅ እና በጥናት እና ምርምር ላይ የተመሰረተ ድጋፍ ለማድረግ የመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን እና የኢትዮጵያ አርብቶ አደሮች ፎረም ተስማሙ፡፡ተቋማቱ የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረሙ ሲሆን በጋራ ሊሰሯቸው የሚችሏቸው ነጥቦች ላይም ተስማምተዋል፡፡የአርብቶ አደሩን  ማህበረሰብ ከወቅታዊ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ የአየር ንብረትን ለመቋቋም የሚያስችሉ የምርምር እና የጥናት ስራዎችን በጋራ ለመሥራት ነው የተስማሙት፡፡

የመለስ ፋውንዴሽን ምክትል ሊመንበር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ፋውንዴሽኑ ለሴት አርብቶ አደሮች ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥልና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡

ለአርብቶ አደሩ ዘላቂነት ያላቸው እቅዶችን እና ወቅቱን የጠበቀ መረጃ እንዲያገኙ በማድረግ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዙሪያ ያለውን ግንዛቤ ማስፋት እንደሚገባም ነው የኢትዮጵያ አርብቶ አደር ፎረም ሊቀመንበር አቶ አብዲ ሁሴን የገለፁት፡፡

በመድረኩ ከሴት አርብቶ አደሮች ጋር በተያያዘ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy