Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ነገ ይጀምራል

0 491

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ ይጀምራል።

የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ባደረሰን መረጃ ለአራት ቀናት በሚቆየው ጉባኤ፥ የበጀት አመቱ ስድስት ወራት የክልሉ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።

የአስፈጻሚ አካላት የተቃለለ የልማትና መልካም አስተዳደር እቅድ፣ የክልሉ የዳኝነት አካላት አፈጻጸም እቅድና የዋናው ኦዲተር መስሪያ ቤት የክዋኔ ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርቶችም ቀርበው ይገመገማሉ።

የምክር ቤቱ አፈጉባኤ አቶ ይርሳው ታምሬ፥ ምክር ቤቱ በየዘርፉ የተፈጸሙ ተግባራትን የሚገመግም ቋሚ ኮሚቴ አቋቁሞ ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ብለዋል።

አፈጻጸሙ ቀርቦም እንደሚገመገምና የህዝብ ጥያቄን መሰረተ ያደረጉ ጉዳዮች ትኩረት እንደሚያገኙ ተገልጿል።

በጉባኤው ለልማት፣ መልካም አስተዳደርና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አጋዠ የሆኑ አዋጆችም ይጸድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy