Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሳዑዲ ጋር የተደረሰውን የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነት አፀደቀ

0 391

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሳዑዲ አረቢያ ጋር የተደረሰውን የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነት አፀደቀ።

አሜሪካ በቀድሞው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ አስዳደር ወቅት አቋርጣው የነበረውን የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነት ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያፀደቀው።

ተንታኞች ሪያድ በየመን በምታደርገው የአየር ላይ ጥቃት ንፁሃንን እየገደለች ነው የሚል ትችት ይሰነዝሩባታል።

ሳዑዲ እና አሜሪካ ባለፈው አመት የ1 ነጥብ 15 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።

ይሁን እንጂ የሳዑዲ የጦር አውሮፕላኖች በየመን በቀብር ስፍራ ላይ ባደረሱት ጥቃት በርካታ ንፁሃን ተገድለዋል በሚል የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ስምምነቱን ውድቅ አድርገውታል።

በስምምነቱ ሳዑዲ ከዋሽንግተን ታንኮች እና ጥይት የማይበሳቸው ተሽከርካሪዎች ለመሸጥ ነበር የተስማማችው።

ሪያድ ከፈረንጆቹ መጋቢት 2015 ጀምሮ በየመን በከፈተችው ዘመቻ ከ12 ሺህ በላይ ሰዎች መሞታቸውን የየመንን ጉዳይ የሚከታተል አጣሪ ቡድን ይፋ አድርጓል።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጦር መሳሪያ ሽያጩን ማፅደቁ የትራምፕ አስተዳደር በየመን ጦርነት ከሳኡዲ ጋር ግንኙነቷን ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ያሳያል እየተባለ ነው።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy