Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአዘርባጃኑ መሪ ሚስታቸውን በምክትል ፕሬዚዳንትነት ሾሙ

0 527

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የአዘርባጃኑ ፕሬዚዳንት ኢሃም አሊየቭ የትዳር አጋራቸውን መህሪባንን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አድርገው መሾማቸውን ባለፈው ማክሰኞ በይፋ ማስታወቃቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ፕሬዚዳንቱ የ52 አመት ዕድሜ ያላቸውን ባለቤታቸውን በአገሪቱ የስልጣን እርከን ሁለተኛ ደረጃን በሚይዘውና ባለፈው መስከረም ወር ላይ በጸደቀው አዲሱ የተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ቦታ ላይ ማስቀመጣቸው ብዙዎችን እያነጋገረ እንደሚገን የገለጸው ዘገባው፣ ዘገባው ገልጧል፡፡ ባለፈው መስከረም ወር
ላይ በተከናወነው ህዝበ ውሳኔ በአገሪቱ የህገ መንግስት አንቀጾች ላይ ማሻሻያ መደረጉን ያስታወሰው ዘገባው፣
የፕሬዚዳንቱን የስልጣን ዘመን ከአመስት አመታት ወደ ሰባት አመታት ማሳደጉ፣ ከ14 አመታት በፊት የአባታቸውን ቦታ ተክተው አገሪቱን መምራት የጀመሩት ፕሬዚዳንት አሊየቭ ከስልጣን ላለመውረድ የያዙት አቋም መገለጫ ነው በሚል መተቸቱንም አክሎ ገልጧል፡፡
በምክትል ፕሬዚዳንትነት የተሾሙት መህሪባን በህክምና ሙያ ከዩኒቨርሲቲ መመረቃቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ከዚህ ቀደም በህግ አውጭነት መስራታቸውንና የአንድ በጎ አድራጎት ድርጅት ሃላፊ ሆነው ማገልገላቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
ገና የ19 አመት ወጣት ሳሉ ከፕሬዚዳንት ኢሃም አሊየቭ ጋር ትዳር የመሰረቱት መህሪባን፣ በረጅም አመታት የትዳር ቆይታቸው ሁለት ሶቶች እና አንድ ወንድ ልጅ ማፍራታቸውን ዘገባው አክሎ ገለጧል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy