Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ምርቶቻቸው በጤና ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ስድስት የውሃና የከረሜላ አምራቾች ንግድ ፈቃድ ተሰረዘ

0 785

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በህብረተሰብ ጤና ላይ ጉዳት ያደርሳሉ ባላቸው ስድስት የከረሜላና የውሃ አምራች ኩባንያዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን የኢትዮጵያ የምግብ፣ መድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለሥልጣኑ በክትትልና ቁጥጥር ስራው ለህብረተሰቡ ጤና አስጊ ናቸው ያላቸውን አራት የከረሜላና ሁለት የታሸገ ውሃ አምራችና አስመጪዎች የንግድ ፈቃድ መሰረዙን ገልጿል።

የባለስልጣኑ የምግብ አምራቾች ቁጥጥር አስተባባሪ አቶ ገረመው ጣሰው እንደገለጹት፥ በድርጅቶቹ ላይ እርምጃ የተወሰደው በ190 ሀገር በቀል የምግብ አምራችና ላኪዎች ላይ ባካሄደው የቁጥጥርና የክትትል ስራ ነው።

“የስድስቱም ድርጅቶች ምርቶች ለህብረተሰቡ ጤና አስጊ ሆኖ በመገኘቱ ከገበያ እንዲወገዱ ተደርጓል” ብለዋል።

የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሳምሶን አብርሃ እርምጃ ከተወሰደባቸው ድርጅቶች መካለከል የከረሜላ አምራችና አስመጪዎቹ ግሪን ሼር፣

ስዊት ወርልድ እና ኢት ፊትስ ሲሆኑ፥ ሪል ወተር እና ገንድሮብ ወተር ደግሞ ሁለቱ ፈቃዳቸውን የተነጠቁ ውሃ አምራቾች ከስድስቱ አምስቱ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የአንዱን ከረሜላ አምራች ስም እንዲናገሩ፥ ኢዜአ ለሁለቱም የተቋሙ ሃላፊዎች ቢያቀርብም መረጃውን እንዳላገኘ ጠቅሷል።

ድርጅቶቹ ከመታገዳቸው በፊት ማስጠንቀቂያ እንደደረሳቸው የተናገሩት አቶ ገረመው ማስጠንቀቂያውን ተቀብለው ለማሻሻል ባለመፈለጋቸው እርምጃው መወሰዱን አስረድተዋል።

በተመሳሳይም ለ16 ምግብ አምራችና አስመጪዎች ባለስልጣኑ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ መስጠቱንም ነው የተናገሩት።

የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ከተሰጣቸው ድርጅቶች ስምንቱ የምግብ አስመጪና ላኪ ሲሆኑ ስምንቱ ደግሞ አምራቾች መሆናቸው ጠቅሰዋል።

ከነዚህ በተጨማሪም 28 የተለያዩ አምራች ድርጅቶች ላይም ምርቶቻቸው ጥራትና ደረጃቸውን ያልጠበቁ በመሆኑ ከተሰራጩበት ገበያ እንዲሰበስቡ በማድረግ እገዳ እንደተጣለባቸው ተናግረዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy