Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በራስ አቅም የሚካሄደው የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሊመጣ የሚችለውን የዲፕሎማሲ ጫና ማቃለል አስችሏል —ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል

0 675

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፊል የግንባታ ስራ በራስ አቅም እየተካሄደ መሆኑ ሊመጣ የሚችለውን የውጭ ጫና እንዳቃለለ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል አስታወቁ።

የትግራይ ብዙሀን መገናኛ ተቋም የህዳሴ ግድብ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበትን ስድስተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በመቀሌ ከተማ ያዘጋጁት የፓናል ውይይት ዛሬ ተካሂዷል፡፡

ሚኒስትሩ በፓናል ውይይቱ ወቅት እንዳሉት፣ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ  ግንባታ ሲታሰብ አብሮት ሊመጣ የሚችል የፋይናንስ፣ የዲፕሎማሲና ሌሎችንም ተፅኖዎች አስቀድሞ መለየት ተችሏል፡፡

በግልገል ጊቤ ሶስት ግድብ የግንባታ ፕሮጀክት ላይ ካጋጠሙት ፈተናዎች ትምህርት በመውሰድ ሥራውን ሙሉ በሙሉ ለውጭ ተቋራጮች ከመስጠት ይልቅ ከፊል ስራዎች በራስ አቅም እየተካሄደ በመሆኑ የተለያዩ ጫናዎችን መቀነስ አስችሏል፡፡

ሚኒስትሩ እንዳመለከቱት ሳሊኒ የሲቪል ስራዎች እንዲያከነውን ሲደረግ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ደግሞ በሃገር መከላከያ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

ይህም ያጋጥም የነበረው የግንባታ መስተጓጎልና የውጭ ምንዛሪን ከመቀነስ ባለፈ ሌሎች ሜጋ ግድቦችን ለመገንባት የቴክኖሎጂና የእውቀት አቅም መገኘቱንም ጠቁመዋል፡፡

የግድቡ ግንባታ አሁን 57 በመቶ የደረሰ መሆኑን ያመለከቱት ዶክተር ደብረጽዮን ፣ ” የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ የሳድል ግድብ፣የኤሌክትሮ ሜከኒካል ስራዎችና ሌሎችን ጨምሮ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

ከተጠናቀቁትም መካከል የሳብስቴሽንና ባለ 500 የሀይል ማስተላለፊያ ግንባታ ይገኝበታል፡፡

የግድቡ ግንባታ በጥሩ ፍጥነትና ምቹ በሆነ ሁኔታ መቀጠሉን ጠቅሰው እስከ አሁንም 50 ቢሊዮን ብር ወጪ መሆኑን ሚኒስትሩ አመልክተዋል፡፡

ሚኒስትሩ በግድቡ ግንባታ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy