Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የኦዲት ግኝት መረጃዎችን ለማጥፋት ሲባል ላፕቶፖችን እስከ መስረቅ የደረሰ ወንጀል እየተፈፀመ ነው ተባለ

0 1,393

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኦዲት ግኝት መረጃዎች ለማጥፋት ሲባል ሰነዱ የተቀመጠባቸውን ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን እስከ መስረቅ የደረሰ ወንጀል እየተፈፀመ መሆኑ ተገልጿል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ ግዥና አሰተዳደር ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኦዲት ቁጥጥር ወቅት ከኦዲት ተደራጊው መስሪያ ቤት ለባለሙያ ተብለው የተሰጡ ቢሮዎችን በመገንጠል የሚፈጸሙ የላፕቶፕ ኮምፒዪተር ስርቆት መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።

እስካሁን ድርጊቱ በአዳማ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን እና በኢትዮጵያ ምግብ፣ መድሀኒትና ጤና ክብካቤ ቁጥጥር ባለስለጣን መስሪያ ቤቶች ተፈፅሟል።

በኦዲት ቁጥጥር ወቅት ለኦዲት ባለሙያው ከተሰጠው ቢሮ ውስጥ የኦዲት ግኝት የሰፈረባቸው የላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ተሰርቀዋል።

የፌደራል ዋና ኦዲተር አቶ ገመቺ ዲቢሶ፥ ስርቆቱን በመፈጸም የተጠረጠሩት ግለሰቦች ለህግ መቅረባቸውን ተናግረዋል።

በተሰረቁት ላፕቶፖች ውስጥ የነበሩት የኦዲት ግኝት መረጃዎች አስተማማኝ በሆነ መንገድ በሌሎችም ስፍራዎች በመቀመጣቸው ምንም አይነት መረጃ አለመጥፋቱንም ዋና ኦዲተሩ አረጋግጠዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy