Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በቆሼ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች መኖሪያ ቤት ተሰጣቸው

0 655

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በቆሼ በደረሰው የአፈር መደርመስ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውና ኃብትና ንብረታቸውን ላጡ ወገኖች የመኖሪያ ቤት ተበረከተላቸው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአደጋው ጉዳት ለደረሰባቸው ነዋሪዎች በንፋስ ስልክ ላፍቶና ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞች ውሰጥ በ24 ሚሊዮን ብር ወጪ የተሰሩ 110 የመኖሪያ ቤቶች ለተጎጂዎች አስርክቧል።

የከተማዋ ከንቲባ ዲሪባ ኩማ የቤቱን ቁልፍ ለተጎጂዎች ባስረከቡበት ወቅት እንዳሉት “የከተማ አሰተዳደሩ በተቻለ አቅም ተጎጂዎቹን የመርዳትና የማቋቋም ስራው ይቀጥላል” ብለዋል።

ቤቶቹ የተገነቡት ለኑሮ ተስማሚ በሆኑ አካባቢዎች በመሆኑ ተጎጂዎች ከህዝቡ ድጋፍ በተጎዳኝ ጠንክሮ በመስራት ኑሯቸውን ማሻሻል አለባቸው ነው ያሉት።

በቆሼ በደረሳው አደጋ ኮልፌ ቃራኒዮ ክፍለ ከተማ አስኮ አዲስ ሰፈር አካባቢ በ16 ሚሊዮን ብር የተገነቡ ቤቶች ለተጎጂ ቤተሰቦች ተብርክተዋል።

በሌላ በኩልም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍል ከተማ በ8 ሚሊዮን ብር ወጭ የተገነቡ ቤቶች ለተጎጂዎቹ የተሰጠ ሲሆን ቤቶቹ የውሃ፣የኤሌክትሪክ፣የመጸዳጃና የምግብ ማብሰያ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው መሆኑ በርክክብ ወቅት ተገልጿል።

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ነዋሪዎችም ህዝብና መንግስት ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን አርቅበዋል።

በአደጋው ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻች እስካሁን በተካሄደው የድጋፍ ማሰባሰብ ስራ 60 ሚሊዬን 998 ሺህ ብር በጥሬ ብር እና ከስድስት ሚሊየን ብር በላይ በዓይነት ድጋፍ ተሰብስቧል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy