Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

አለም አቀፉ የፈጣን ምግቦች አምራች ኩባንያ ያም በኢትዮጵያ 10 ቅርንጫፎች ሊከፍት ነው

0 404

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የዩናይትድ ስቴትስ ግዙፉ ያም ብራንድስ አለም አቀፍ ኩባንያ እና የኢትዮጵያው በላይ አብ ፉድስ እና ፍራንቻይዝ ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ በኢትዮጵያ 10 የፒዛ ምግቦች የሚሸጡባቸው ሬስቶራንቶች ለመክፈት ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

የመጀመሪዎቹ ሶስቱ በስድስት ወራት ስራ የሚጀምሩ መሆናቸውን እና በሶስት አመታት ጊዜ ውስጥ 10 የፒዛ ቤቶች እንደሚከፈቱ የፕሮጀክቱ ባለአክስዮን ሚካኤል ገብሩ ለሬውተርስ ተናግረዋል።

መቀመጫውን ኬንታኪ ያደረገው ያም በአፍሪካ ከ1 ሺህ በላይ የፒዛ ምግቦች ሬስቶራንቶች ደረጃውን ጠብቀው በመለያው የሚሸጡ ሲሆን፥ ኩባንያው በአህጉሪቱ 188 ፍቃድ ያላቸው ቅርንጫፎች እንዳሉት ተዘግቧል፡፡

ያም ብራንድስ በአሜሪካ እና በመላው አለም ፈጣን ምግቦችን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፥ 42 ሺህ 692 ሬስቶራንቶች የፈጣን ምግብ ምርቶችን በኩባንያው ደረጃ እና መለያ የሚሸጡ መሆናቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

ከተጠቀሰው ቁጥር ውስጥ 8 ሺህ 927 የሚሆኑት በኩባንያው በቀጥታ በባለቤትነት የሚተዳደሩ ናቸው።

ምንጭ፦ ሬውተርስ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy