Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

0 333

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን ከሚያዝያ 24 ጀምሮ ኢትዮጵያን ለሶስት ቀናት ይጎበኛሉ፡፡

ኮሚሽነሩ የኢፌዴሪ መንግሥት ባደረገላቸው ግብዣ መሰረት ሀገሪቱን እንደሚጎበኙ ታውቋል፡፡

እግረ መንገዳቸውን ከአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጋር እንደሚወያዩም ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ ቆይታቸው የሀገሪቱን የሰብአዊ መብት ሁኔታና የመንግሥታቱን ድርጅት የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ተግባራት በተመለከተ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣

ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አባዱላ ገመዳና ከሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጋር ምክክር ያደርጋሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ኮሚሽነሩ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር አዲሱ ገብረእግዚአብሔር፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶችና ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተገናኝተው እንደሚነጋገሩም ታውቋል፡፡

ኮሚሽነር ዘይድ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማትን ጨምሮ ከህብረቱ የሰላምና ደህንነት ኮሚሽነር ስማይል ቼርጉይና ከህብረቱ የፖለቲካ ጉዳዮች ኮሚሽነር ሴሱማ ሚናታ ሳማቴ ጋር ተገናኝተው የሁለቱን ተቋማት የሰብዓዊ መብቶች ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ያደርጋሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በቅርቡ በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የተጠናከረ ትብብር ለማድረግ በኒዮርክ በተፈረመው የስምምነት ትግበራና መሰል የትብብር ዘርፎች የውይይታቸው አጀንዳዎች እንደሚሆኑም ተገልጿል፡፡

ኮሚሽነሩ በጉብኝታቸው ማጠቃለያ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የስብሰባ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡም በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን ቢሮ ይፋ ማድረጉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy