Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተመረጡ የቱሪዝም መስኮች ሊሰማሩ ነው

0 409

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ ባለሃብቶች በኢትጵያ በተመረጡ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ለመስራት ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር ተወያይተዋል፡፡

ባለሃብቶቹ በዋናነት በባህልና ቱሪዝም ዘርፍ ለመሰማራት ባላቸዉ ፍላጎት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ቢሆንም፥ በሌሎች የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይም ሰፊ ውይይት ከሚኒስቴሩ ጋር አድርጓል።

የትግራዩ አልነጃሽ መስጊድ፤ የሰሜንና ባሌ ተራሮች፤ ሃረሪና አዲስ አበባ ለልኡኩ ከቀረቡ የተመረጡ ስፍራዎች መካከል ይጠቀሳሉ።

በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር አብዱልቃድር ርዝቁ እንዳሉት፥ ባለሃብቶቹ በቱሪዝም ዘርፉ የካበተ ልምድ ካለው ሃገር የመጡ ናቸዉ።

ይህንን ተሞክሮ ወደ ሃገራችን በማምጣት በዘርፉ ያለውን የቱሪስት ቁጥር ለማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ እድልን ለማስፋትና የውጭ ምንዛሪን ለማሳደግ ባለሃብቶቹ በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ እየሰራን ነው ብለዋል።

አንድ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ባለ ሃብት በአዲስ አበባ ከተማ በሆቴል ግንባታ ስራ ላይ መሰማራቱንም አምባሳደሩ ጨምረው ተናግረዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy