Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የታላቁ ህዳሴ ግድቡ የአርማታ ሙሌት 72 በመቶ ተጠናቋል-ኢንጅነር ስመኘው

0 545

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋናው ግድብ የአርማታ ሙሌት 72 በመቶ መጠናቀቁን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ ገለጹ፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹን ኢንጅነር ስመኘው በዋናው ግድብ ከሚጠበቀው 10 ነጥብ 2 ሚልዮን ኪዩብ የአርማታ ሙሌት 7 ነጥብ 3 መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡

ከአርማታ ሙሌቱ ጎን ለጎን በግድቡ ቀኝ ክፍል የሚገኙት 10 ዩኒቶችና በግድቡ ግራ ክፍል የሚገኙት 6 ዩኒቶች ፊት ለፊት የሀይል ክፍሎች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ኢንጅነር ስመኘው ተናግረዋል፡፡

በሳድልና ጉባ ተራራዎች ባለው 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ዋና ግድብ ከተገነባ በኃላ 246 ኪ.ሜ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ወደ ኃላ እንዲተኛ ይደረጋል ብለዋል ኢንጅነር ስመኘው፡፡

በግድቡ አማካኝነት የሚጠራቀመው 74 ሚልዮን ኪዩብ ውሃ 16 ዩኒቶች ላይ የተገጠሙ ጄኔሬተሮችን ካንቀሳቀሰ በኃላ ውሃው ወደ ታችኛው ተፋሰስ እንደያልፍ ይደረጋል ብለዋል ስራ አስኪያጁ ኢንጅነር ስመኘው፡፡

ከውሃ መስተላለፊያ ቱቦዎች በተጨማሪ ለታችኛዎቹ ተፋሰስ አገራት 6 ሜትር ስፋት ያላቸው የውሃ ማስተንፈሻ ቱቦዎች በኢፌዴሪ ብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ እየተገነቡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy