Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የአፍሪካ ትልቁ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው

0 1,402

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በአፍሪካ ትልቁ የተባለና “ህዳሴ ግራንድ ሞል” በሚል ስያሜ የሚጠራ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው።

ግንባታው በአገር ውስጥ ባለሃብቶች በተቋቋመው ህዳሴ አክሲዮን ማህበር በሶስት ቢሊዮን ብር ይከናወናል ተብሏል።

ይህ በአፍሪካ በአይነቱ የመጀመሪያ የተባለው ግዙፍና ዘመናዊ የገበያ ማዕከል በ125 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ የሚያርፍ ሲሆን ጠቅላላ የግቢው ስፋት 250 ሺህ ካሬ ሜትር ይሸፍናል።

የህዳሴ ግራንድ ሞል ስራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ መኮንን በሰጡት መግለጫ የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ከሚገኙት በስፋቱና በዘመናዊነቱ የላቀ ነው።

ግንባታው የከተማ አስተዳደሩ ለአክሲዮን ማኅበሩ ካመቻቻቸው ዘጠኝ ቦታዎች በአንዱ ላይ ይከናወናል።

የገበያ ማዕከሉ በውስጡ 5 ሺህ ሱቆች፣ 2 ዘመናዊ ባለ 4 ኮከብ ሆቴሎች፣ ባንክና ኢንሹራንስ፣ ካፌና ሬስቶራንቶችን የሚይዝ ነው።

ማዕከሉ በአንድ ጊዜ 8 ሺህ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ የፓርኪንግ አገልግሎት መስጫ እንዲሁም የመኖሪያ አፓርታማዎች እንደሚኖሩትም ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል።

ግንባታው ሲጠናቀቅ ለ35 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል እንደሚፈጥር የገለጹት አቶ ደረጀ፤ ነጋዴውና ሸማቹ ግብይታቸውን በአንድ ቦታ እንዲከውኑ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

ግንባታውን ለማስጀመር ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ ለማወዳደር ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

የገበያ ማዕከሉ ግንባታ በሶስት ዓመት ጊዜ ተጠናቆ ስራ አንደሚጀምርም አቶ ደረጀ ጠቁመዋል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy