Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የኢትዮ-ጃፓን የቢዝነስ ፎረም ዛሬ በቶኪዮ ይካሄዳል

0 419

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የኢትዮጵያ እና የጃፓን የቢዝነስ ፎረም ዛሬ በቶኪዮ ይጀመራል፡፡

በኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ አብተው የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክም ጃፓን ገብቷል፡፡

ፎረሙ በማምረቻ ኢንዱስትሪ እድገት ላይ አተኩሮ እንደሚመክር ተጠቁሟል፡፡

በኢትዮጵያ እያደገ የመጣው የማምረቻ ኢንዱስት ዘርፍ እና የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበር ላይ የኢትዮጵያ እና የጃፓን ትብብር ለዘርፉ እድገት በሚኖረው አስተዋፅኦ ላይ ውይይት ይደረጋልም ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ እና ጃፓን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነታቸውን የሚያጠናክር አዲስ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

ethio-japan_signed_MOU.jpg

የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት እና የጃፓኑ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ናቸው ስምምነቱን የተፈራረሙት፡፡

ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ትስስር እና የንግድ ዲፕሎማሲ ቀጣይ እንዲሆን እና እንዲጠናከር አዲስ በር ከፋች ነው ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አፈወርቅ፥ የመግባቢያ ስምምነቱ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ማህበረሰብ ተግባራዊ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ትስስር እና ተጠቃሚነት እንደ አዲስ የሚፈጥሩበት ነው ብለዋል፡፡

የጃፓን የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ቶሩ ኢሺዳ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ በሰው ሃይል ልማት ላይ እየሰራች መሆኗን አድንቀዋል፡፡

ስምምነቱ በሁለትዮሽ የንግድ ስርዓቱ እና በኢንቨስትመንት ላይ መረጃዎችን ለመለዋወጥና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመለየትና በጋራ ለመፍታት እንደሚያስችል ነው የተነገረው፡፡

 

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy