Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

የግድቡ ግንባታ ለጋራ ተጠቃሚነት አርቆ አሳቢነትን ያበሰረ ነው – አቶ ደመቀ መኮንን

0 321

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የግድቡ ግንባታ ለወዳጅና ጎረቤት ሃገራት የጋራ ተጠቃሚነትንና አርቆ አሳቢነትን ያበሰረ መሆኑን የግድቡ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ሰብሳቢ አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ።

የግድቡ ግንባታ የተጀመረበት ስድስተኛ ዓመት ክብረ በዓል በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ጉባ ወረዳ “የታላቁ ህዳሴ ግድባችን የሀገራችን ሕብረ ዜማ የህዳሴያችን ማማ” በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ተከብሯል።

አቶ ደመቀ በዚህ ጊዜ እንዳሉት፥ የህዳሴው ግድብ የኢትዮጵያን የሃይል ፍላጎት ጥያቄ ከመመለስ ባሻገር የምስራቅ አፍሪካ ሃገራትን የኃይል ፍላጎት የሚያሟላና የአካባቢውን ስነ ምህዳር የሚጠብቅ ጉልህ አህጉራዊ ፕሮጀክት ነው።

በኢትዮጵያውያንና በመንግስት ሃብት እየተገነባ ያለው ይህ ግድብ በብዙ መንገድ ለጋራ ጥቅም እንደምንሰራ ያረጋግጣልም ብለዋል አቶ ደመቀ።

የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ ህብረተሰቡ በተለያዩ መንገዶች ተግባራዊ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሰው፥ የክልሎች እየተዘዋወረ ያለው የህዳሴ ግድብ ዋንጫ ከ 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማስገኘቱን አንስተዋል።

ግንባታው የፈጠረው ሃገራዊ ንቅናቄ ከግድቡ አልፎ በሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችም በህዝቡ ዘንድ ዳር የማድረስ ቁጭት እንዲፈጥር አድርጓልም ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አዜብ አስናቀ በበኩላቸው፥ ግድቡ በሃገሪቱ እየጨመረ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት በተገቢው መንገድ ለማስተናገድ ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።

መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው የላቀ ትኩረት በርካታ ፕሮጀክቶች ተቀርጸው እየተሰሩ ነው ያሉት ስራ አስፈጻሚዋ፥ የህዳሴው ግድብም ዋነኛ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እንደሚሆን ገልጸዋል።

ከኢንዱስትሪ ፓርኮችና ግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ግንባታ መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሃይል ፍላጎቱ በዚያው ልክ በየአመቱ እያደገ በመሆኑ ግድቡ ክፍተቱን በመሙላት የማይተካ ሚና እንዳለው ጠቅሰዋል።

የግድቡ ግንባታ በተደረገለት የማሻሻያ ሥራ ኃይል የማመንጨት አቅሙ ወደ 6 ሺህ 450 ሜጋ ዋት ከፍ ማለቱን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy