Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ደቡብ አፍሪካ የኒዩክሌር ሀይል ማመንጫዎችን ለመገንባት የደረሰችው ስምምነት ውድቅ ተደረገ

0 1,158

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀገሪቱ መንግስት የኒዩክሌር ሀይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ለመገንባት ከሶስት ሀገራት ጋር የደረሰውን ስምምነት ውድቅ አደረገ።

ደቡብ አፍሪካ ስምምነቱን ከሩስያ፣ አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ ጋር ነበር የተፈራረመችው።

የኬፕ ታውን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ስምምነቱን ህግን የጣሰ ነው በሚል ውድቅ አድርጎታል።

መንግስት የኒዩክሌር እቅዱን ለህዝብ ውይይት አለማቅረቡ እና በፓርላማ ክርክር ሳይደረግበት መቅረቱንም ነው ፍርድ ቤቱ የጠቀሰው።

ኧርዝላይፍ አፍሪካ ኤንድ ሳውዝ አፍሪካን ፌዝ ኮሚዩኒቲስ ኢንቫይሮመንታል ኢንስቲትዩት ከሶስቱ ሀገራት ጋር የተደረሰውን የኒዩክሌር ስምምነት ወደ ፍርድ ቤት በመውሰዱ ነው ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው።

የሀገሪቱ መንግስት እስካሁን በፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ ምንም አይነት አስተያየት አልሰጠም።

ደቡብ አፍሪካ ስምንት የኒዩክሌር ሀይል ማመንጫ ጣቢያዎችን በ1 ትሪሊየን ራንድ (76 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር) ለመገንባት ማቀዷ ይታወሳል።

ይህ የሀገሪቱ እቅድም በአየር ንብረት ለውጥ ተሟጋቾች ሲተች የቆየ ቢሆንም፥ የሀገሪቱ መንግስት እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ሀይል ፍላጎት ለማሟላት ከድንጋይ ከሰል ይልቅ የኒዩክሌር ሀይል እንደሚያስፈልግ ይሞግታል።

ደቡብ አፍሪካ በአህጉሪቱ ብቸኛዋ የኒዩክሌር ሀይል ማመንጫ ያላት ሀገር መሆኗን ቢቢሲ በዘገባው አስታውሷል።FBC

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy