Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

በዘላቂ ልማት ላይ ያተኮረ አህጉራዊ ጉባዔ በመጪው ሳምንት በአዲስ አበባ ይካሄዳል

0 326

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

በዘላቂ ልማት ላይ ያተኮረ አህጉራዊ ጉባዔ በመጪው ሳምንት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

ጉባዔው “ሁሉን አሳታፊ ዘላቂ ልማትና ብልጽግና ለሁሉም” በሚል መሪ ሃሳብ ከግንቦት 9 እስከ 11 2009 ዓ.ም በአፍሪካ ኅብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል።

የአፍሪካ ሃገራት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችና የ2063 አጀንዳ ተፈጻሚነት ላይ መወያየት የጉባዔው ዋነኛ አጀንዳ ይሆናል ተብሏል።

በ2017 ለማሳካት የታቀዱና የ2063 አጀንዳ የመጀመሪያ 10 ዓመት ግቦች ማሳካትን አስመልክቶም ውይይት ይካሄዳል።

ድህነትን በማስወገድ ኢኮኖሚያዊ እድገት ማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የሚካሄድ ምክክርም ሌላው የውይይቱ አጀንዳ ነው።

ተሳታፊዎች “ሁለቱን የልማት ግቦች ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ያሉ ዕድሎችና ፈተናዎች ምንድን ናቸው?” በሚል ርዕስ እንደሚመክሩም ይጠበቃል።

ከጉባዔው ጎን ለጎን ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር አባላት በዘላቂ ልማት ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ።

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን፣ የመንግስታቱ ድርጅት፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ተቋማት፣ የልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት በጉባዔው እንደሚሳተፉ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ድረ-ገጽን ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል።

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy