Ethiopiaprosperous
Ethiopian News Ethiopian Daily news, Regarding political and social Issues.

ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ማስፋት እንደምትፈልግ ገለጸች

0 633

Get real time updates directly on you device, subscribe now.

የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ አጠቃላይ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ከፍ ማድረግ እንደምትፈልግ ገለጹ።

ፕሬዝዳንቱ  ይህን የገለጹት በበጂንግ ለሚካሄደው አለም አቀፉ “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” ፎሮም ላይ ለመሳተፍ  በጂንግ ከገቡት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።

ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ በአዲሱ የአለም የኢኮኖሚ አሰላለፍ፤ ዘመናዊ ዕድገትና ልማትን በማጣመር ፍትሃዊና ዘመናዊ ዕድገትን ለማምጣት ያለመ ነው፡፡

ግንቦት 6 እና 7 በቤጂንግ በሚካሄደው የኢኒሴቲቩ ፎረም ላይ ከአንድ መቶ አስር በላይ አገራትና ከሀያ ስምንት በላይ የአገራት መሪዎች እንደሚሳተፉበት ይጠበቃል።

ኤኒሼቲቩ እ.ኤ.አ እስከ 2050 የአለምን 80 በመቶ ጠቅላላ አገራዊ ምርት አስተዋፅኦ በማበርከት ከሶስት ቢሊዮን በላይ ለሚሆኑ ህዝቦችም መካከለኛ ገቢ እንዲኖራቸው ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፤ ሺንዋ

Leave A Reply

Your email address will not be published.

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy